
ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን
Debre Teamrat Dagmawit Tsadkane Saint Mary's Church
የደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በ1996ዓ.ም በባሕታዊ ገብረ ማርያ ደበሌ ተመስርታለች። ሆኖም ሰንበት ትምህርት ቤት ባለመቋቋሙ በሚከበረው የጥምቀት በዓል ታቦተ ህጉን አጅብው በዝማሬና በተለያዩ አገልግሎቶች የሚሸኙ ወጣቶች አለመኖራቸውን የተመለከቱ የአከባቢው ወጣቶች በቤተ ክርስቲያን ግቢ እንዲሁም በአቅራቢያው በሚገኙ ቤቶች…


Sunday School
Debre Teamrat Dagmawit Tsadkane Saint Mary's Church
የእኛ ተልእኮ፣ ራእይ እና ዓላማ
ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለማህበረሰቡ የሚያቀርበውን የመንፈሳዊ እና ማህበራዊ አላማ ከታች በግልፅ መልኩ አቀርበናል።
<p> 1. በአጥቢያው የሚገኙ ወጣቶች እና ሕፃናትን ትክክለኛውን የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ትምህርተ ሃይማኖት እና የአብነት ትምህርት በማስተማር የቤተክርስቲያኗን ዶግማ፣ሥርዓት፣ትውፊት፣ታሪክ እና ወቅታዊ ሁኔታ እንዲያውቁ ማድረግ፣ ወጣቶች ምዕመናን በሃይማኖት መሰል መናፍቃን እንዳይወሰዱ መጠበቅ</p>
<h2> አላማ</h2><p>በአጥቢያው የሚገኙ ወጣቶች እና ሕፃናት በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ እምነት እና ሥርዓት የሚሄዱ ሆነው በእውቀታቸው፣ በገንዘባቸው፣ በጉልበታቸው በሞያቸው እንዲሁም በክህነታቸው ሲያገለግሉ እና በዓላማዊው በአስኳላው ትምህርታቸው <br>ውጤታማ ሆነው ማየት፣</p>
<h2> እሴቶቻችን</h2><p> ፈሪሃ እግዚአብሔር ፣ ተጠያቂነት ፣ ፍቅር የሆነ አገልግሎት ፣ ትህትናና መታዘዝ ፣በመከራ ሁሉ መጽናት፣ ለሰማያዊ ዋጋ መትጋት ፣ ሁሉን በእኩልነት መገልገል፣ ዘመኑን መዋጀት</p><p><br></p>
ስለ ሰንበት ት/ቤቱ
ለሁሉም እድሜ ደረጃ እምነት፣ ትምህርት እና አስተባበር ማሳደግ
ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን
ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
ስለ አመሰራረቱ
ስለ እኛ
የደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በ1996ዓ.ም በባሕታዊ ገብረ ማርያ ደበሌ ተመስርታለች። ሆኖም ሰንበት ትምህርት ቤት ባለመቋቋሙ በሚከበረው የጥምቀት በዓል ታቦተ ህጉን አጅብው በዝማሬና በተለያዩ አገልግሎቶች የሚሸኙ ወጣቶች አለመኖራቸውን የተመለከቱ የአከባቢው ወጣቶች በቤተ ክርስቲያን ግቢ እንዲሁም በአቅራቢያው በሚገኙ ቤቶች ተሰባብስበው ዝማሬያትን ማጥናት፣ ስለበዓሉ አከባበር የተለያዩ ውይይቶችን በማድረግ ዝግጅታቸውን ጀመሩ ።ይህም የካቲት 19 1996 ዓ.ም የሰንበት ትምህርት ቤታችን የፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት መነሻ ነበር።

ስለ ቤተክርስቲያኑ ታሪክ እና መግለጫ
ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መቼና እንዴት ተመሰረተች ?
ከቀድሞ ዘመን ጀምሮ የነበሩ የእግዚአብሔር ልጆች ስመ ክርስትና የሚያገኙበት የእግዚአብሄርን ቃል የሚሰሙበት ከፈጠሪያችን ከእግዚአብሔር ጋር በጸሎት የሚገናኙበት ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን የሚቀበሉበት አረፍተ ዘመን ሲገታቸው የሚያርፉበት ቤተ ክርስቲያን ሲተክሉ ቆይተዋል። በመሆኑ የደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በቅዱስ እግዚአብሔር ፈቃድ መጋቢት 29 ቀን 1993 ዓ.ም ጀምሮ ለ3 ዓመታት በገዳም ስርዓት ጫማ ከቅጽር ግቢ አውጥቶ በመግባት በጸሎት ሕሙማን ከተለያዩ በሽታዎች ከኤች አይቪ ኤድስ፣ ከአስም እንዲሁም ከአጋንንት በማውጣት የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ በጉልህ የታየበት እንደነበር ይታወቃል። በቦታው የሚጠቀሙ ምዕመናን ቁጥር እየጨመረ ሲመጠ የቅዱስ እግዚአብሔር ፈቃድ ሲደርስ ታህሣሥ 21 ቀን 1996 ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ በነበሩት በብጹዕ አቡነ ኤርሚያስ አማካኝነት ተባርኮ ቅዳሴ ቤቷ ተከብሯል። በቦታው በሚታዩ ድንቅ ድንቅ ተአምራትም የተነሳ ቦታው ደብረ ተአምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ቅድስት ማርያም የሚል ስያሜን ማግኘት ችሏል።
የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
ያግኙን
የሰንበት ትምህርትቤቶች አንድነትን ለማግኘት ከፈለጉ ከታች ያሉትን አድራሻዎች በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ
ስልክ
+251911111111
ኢሜል
finotebrihan@gmail.com
ሁኔታ
Active
አድራሻ
አድራሻ መረጃ አልተገኘም
ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እና አስተያየት ከታች ያለውን ፎርም ይጠቀሙ
Location
አካባቢ
Address
Ethiopia