
ብሔረ ጽጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያም እና መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን
Bhere Tsige Mekane Selam Holy Mary and Medhanealem Church
ሰንበት ት/ቤታችን ፍኖተ ብርሃን እስከካሁን ባሳለፈችው በርካታ ዓመታት ውስጥ በቃለ እግዚአብሔር ልጆችዋን ኮትኩታ በማሳደግ ለወግ ለማዕረግ በማብቃት ሕፃናትን ወጣቶችንና ምዕመናንን /ወላጆችን/ በማስተማር ለስብከተ ወንጌል መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጋለች፡፡በርካታ የሚሆኑ የማኀበሩ አባላት ከሕፃንነታቸው ጀምሮ ሊያድጉባት ለንስሐ ለሥጋ ወደሙ ለመንኩሰና እንዲበቁ እንዲሁም ጋ…


Sunday School
Bhere Tsige Mekane Selam Holy Mary and Medhanealem Church
10 • ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ • አ.አ
የእኛ ተልእኮ፣ ራእይ እና ዓላማ
ብሔረ ጽጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያም እና መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ለማህበረሰቡ የሚያቀርበውን የመንፈሳዊ እና ማህበራዊ አላማ ከታች በግልፅ መልኩ አቀርበናል።
<blockquote>ሕፃናት እና ወጣቶች ቃለ እግዚአብሐርን ተምረው ወላጆቻቸውንና ታላላቆቻቸውን እንዲያከብሩ፣ በአጠቃላይ በሃይማኖት በስነ-ምግባር ታንፀው እንዲያድጉና ለሃገርና ለወገን መልካም ዜጎች እንዲሆን ማድረግ፣</blockquote>
<blockquote> የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ስርዓትና ትውፊት ጠብቆ ሳይለወጥ፣ ሳይበረዝ በቀጥታ ለትውልድ ማስተላለፍ፣ ሕፃናት እና ወጣቶች በሰንበት ት/ቤት ተሰብስበው እየተማሩ ነገረ ሃይማኖት እንዲሁም የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሆነ የሀገርን ታሪክ በሚገባ አውቀው ቤተክርስቲያንን እና ሀገርን ለመረከብ ብቁዎች እንዲሆኑ ማድረግ።</blockquote>
<blockquote><strong>በበጎነተም እውቀትን፤ በእውቀትም ራስን መግዛት፤ ራስን በመግዛት መጽናትን፤ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል፤ እግዚአብሔርን በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፤ በወንድማማች መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ፡፡” 2ኛ ጴጥሮስ 1፤4-7</strong></blockquote>
ስለ ሰንበት ት/ቤቱ
ለሁሉም እድሜ ደረጃ እምነት፣ ትምህርት እና አስተባበር ማሳደግ
ብሔረ ጽጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያም እና መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን
ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ትምህርት ቤት
ስለ አመሰራረቱ
ስለ እኛ
ሰንበት ት/ቤታችን ፍኖተ ብርሃን እስከካሁን ባሳለፈችው በርካታ ዓመታት ውስጥ በቃለ እግዚአብሔር ልጆችዋን ኮትኩታ በማሳደግ ለወግ ለማዕረግ በማብቃት ሕፃናትን ወጣቶችንና ምዕመናንን /ወላጆችን/ በማስተማር ለስብከተ ወንጌል መስፋፋት ከፍተኛ አስተዋፅኦ አድርጋለች፡፡በርካታ የሚሆኑ የማኀበሩ አባላት ከሕፃንነታቸው ጀምሮ ሊያድጉባት ለንስሐ ለሥጋ ወደሙ ለመንኩሰና እንዲበቁ እንዲሁም ጋብቻቸውን በሥርዓተ ተክሊል በቅዱስ ቁርባን እንዲፈጽሙ በማስተማር ለክብር አብቅታለች ዛሬም ቢሆን ከቀድሞው በበለጠና በተጠናከረ ሁኔታ መንፈሳዊ ጉዞዋን በመቀጠል ለተተኪው ትውልድ አስፈላጊውን ሁሉ በማድረግ ላይ ትገኛለች፡፡

ስለ ቤተክርስቲያኑ ታሪክ እና መግለጫ
ብሔረ ጽጌ መካነ ሰላም ቅድስት ማርያም እና መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በ፲፱፻፹፮ ዓ.ም ተመሠረተ
የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
ያግኙን
የሰንበት ትምህርትቤቶች አንድነትን ለማግኘት ከፈለጉ ከታች ያሉትን አድራሻዎች በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ
ስልክ
+251912901245
ኢሜል
fenote_birhan@eotcssu.et
ሁኔታ
Active
አድራሻ
10 • ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከ • አ.አ
ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እና አስተያየት ከታች ያለውን ፎርም ይጠቀሙ
Location
አካባቢ