
ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
Kolfe Keranyo Sub City Sunday Schools Unity
ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የጾታ ልዩነት ሳይደረግ መንፈሳዊ ወጣቶች በዕለተ ሰንበት፣ በዓበይት በዓላትና በአመቺ ጊዜ ሁሉ በየአጥቢያው ቤተ ክርስቲያን እየተገኙ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዐት ምግባር የሚያጠኑበት ትምህርት ቤት ነው ፡፡ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በጉዞዋ ሁሉ ሕፃናቱን፣ ወጣቱን፣ ጎልማሳው እና አረጋዊያንን በማጣመር መንፈሳዊና ሀገራ…


Sub City
Kolfe Keranyo Sub City Sunday Schools Unity
ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ • አዲስ አበባ
የእኛ ተልእኮ፣ ራእይ እና ዓላማ
ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ለማህበረሰቡ የሚያቀርበውን የመንፈሳዊ እና ማህበራዊ አላማ ከታች በግልፅ መልኩ አቀርበናል።
<p>በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ውስጥ ባሉ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በትምህርተ ሃይማኖት፣ በሥርዓተ ቤተክርስቲያን፣ በኢትዮጵያና በዓለም የክርስትና ታሪክ፣ በቤተክርስቲያን የአብነት ትምህርቶች፣ በቤተክርስቲያን አገልግሎት ምስጢራዊ አፈጻጸም ፣በተቀደሰ ትውፊት ላይ ወጥነትና ተከታታይነት ያለው እውቀትን ማስተላለፍ። </p>
<p>የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ምእመናን በተለይም ሕፃናት አዳጊዎችን እና ወጣቶች በነገረ ሃይማኖት ልቀው፣ የተመሟላ ስብእና ይዘው አርአያነት ያላቸው ጉልህ ሃይማኖታዊ እና ሀገራዊ ድርሻ የሚወስዱ፣ አባቶቻቸውን የሚተኩ፣ እና በሀገራዊ ሆነ በዓለም አቀፋዊ የለውጥ ክስተቶች ላይ በጎ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችል ብቁ ትውልድ ሆነው ማየት። </p>
<p>እግዚአብሔርን መፍራት ፣ ሰውን ማክበር ፣ በፍቅር የሆነ አገልግሎት ፣ ክርስቲያናዊ ኃላፊነትና ተጠያቂነት፣ ሁሉን በጥበብና ለመንፈሳዊ ዋጋ ማድረግ ፣ ዓለም ዐቀፋዊ አገልግሎትን ማስፋት ፣ ፅናትና ምስክርነት ፣ ዘመኑን መቅደም፣ መዋጀት። </p>
ስለ አንድነቱ
ለሁሉም እድሜ ደረጃ እምነት፣ ትምህርት እና አስተባበር ማሳደግ
ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
Kolfe Keranyo Sub City Sunday Schools Unity
ስለ አመሰራረቱ
ስለ እኛ
ሰንበት ትምህርት ቤት ማለት የጾታ ልዩነት ሳይደረግ መንፈሳዊ ወጣቶች በዕለተ ሰንበት፣ በዓበይት በዓላትና በአመቺ ጊዜ ሁሉ በየአጥቢያው ቤተ ክርስቲያን እየተገኙ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን እምነትና ሥርዐት ምግባር የሚያጠኑበት ትምህርት ቤት ነው ፡፡ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን በጉዞዋ ሁሉ ሕፃናቱን፣ ወጣቱን፣ ጎልማሳው እና አረጋዊያንን በማጣመር መንፈሳዊና ሀገራዊ ልማት ስታካሒድ ኖራለች፤ በተለይም ደግሞ በትምህርት ዘርፍ ወጣቱን ከሕፃንነቱ ጀምሮ በማስተማር ለሰው ልጅ በሚያፈልጉት የአአምሮና የመንፈስ እድገት የተሟላ እንዲሆኑ ስትሠራ ቆይታለች፤ ወደፊትም ትሠራለች::

የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
ያግኙን
የሰንበት ትምህርትቤቶች አንድነትን ለማግኘት ከፈለጉ ከታች ያሉትን አድራሻዎች በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ
ስልክ
+251954972823
ኢሜል
kolfeandnet@gmail.com
ሁኔታ
Active
አድራሻ
ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ • አዲስ አበባ
ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እና አስተያየት ከታች ያለውን ፎርም ይጠቀሙ
Location
አካባቢ