Blogs & Articles

የክ/ከተማችን አንድነት ወቅታዊ እንቅስቃሴ
Active
ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም
የክ/ከተማችን አንድነት ወቅታዊ እንቅስቃሴ
በሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከግንቦት 1/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ሁሉም ሰ/ት/ቤቶች ሥራ አመራር መርጠው እንዲያጠናቅቁ ከፍተኛ ሥራ እየተሠራ ይገኛል። በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከ ከተማ ያሉ 👉 27ቱም ሰ/ት/ቤቶች የሥራ አመራር አስመራጭ ኮሚቴ መርጠዋል :: 👉 እስከ ሰኔ 7/2018 ዓ.ም ድረስ ሰባት (7) አጥቢያዎች (ሰ/ት/ቤቶች) የየደብሩ ሰበካ ጉባኤ እና የክ/ከ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ተወካዮች በተኙበት የሥራ አመራር ምርጫ አከናውነዋል። 👉 በቀጣይ ሰኔ 14 እና ሰኔ 21/2018 ዓ.ም ምርጫ የሚያከናውኑ ሰ/ት/ቤቶች ያሉ ሲሆን የቀሩት ሁሉም ሰ/ት/ቤቶች ሰኔ 28/2018 ዓ.ም የሥራ አመራር አባላትን መርጠው ያጠናቅቃሉ፡፡ 📌ክ/ከ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ሂደቱ ሰላማዊ ሆኖ ተጀምሮ በተሰካ ሁኔታ እንዲቀጥል ፤ የአስመራጭ አባላት ሲመረጡ፣ የእጩ ጥቆማ ሲቀበሉ ፣ እጩ ሥራ አመራር በማስተቸት ሂደት ላይ እንዲሁም ሥራ አመራር ያስመረጡ ደግሞ ሰላማዊ የምርጫ ሁኔታ እንዲኖር ላደረጉ የየሰ/ት/ቤቱ የጽ/ቤትንና የሥራ አመራር አባላትን አመስግኗል ። 📌 ያላሰመረጡም ሰ/ት/ቤቶች በዚሁ መንፈሳዊ ትጋታቸው እንዲቀጥሉ እና ምርጫው በሰላም እንዲከናወን የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንዲያደርጉ በታላቅ አክብሮት ጠይቋል። 📌 በቀጣይም ሰላማዊና ፍጹም መንፈሳዊ በሆነ መልኩ የኃላፊነት ርክክብ እንዲያደርጉ ፣ አገልግሎታችንም እግዚአብሔር የሚከብርበት እንዲሆን መልዕክቱን አስተላልፏል ! የአቃ/ቃ/ ክ/ከ ሰ/ት/ቤቶች አንድ ነት
በክፍለ ከተማቸን የሚገኙ ሰ/ት/ቤቶቸ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ የሥራ አመራር መርጫ እያከናወኑ ይገኛሉ
Active
ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
በክፍለ ከተማቸን የሚገኙ ሰ/ት/ቤቶቸ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ የሥራ አመራር መርጫ እያከናወኑ ይገኛሉ
በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሥር ከሚገኙ ከ/ክተሞች አንድነት አንዱ በሆነው በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ቅዳሜ በ13/10/2018ዓ.ም እና እሑድ በ14/10/2018 ዓ.ም 5(አምስት) አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሥራ አመራር ምርጫ አከናውነዋል። 1.ቂሊንጦ መካነ ፍስሃ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት 2. አቃቂ መካና ደብረ ብስራት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት 3.ቱሉ ዲምቱ ደብረ መዊዕ ቅዱስ ገብርኤልቤ/ክ ሰ/ት/ቤት  4.ሐመረ ወርቅ ቅ/ማርያም እና ቅድስት አረሴማ ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት 5. ሳሪስ ዳማ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ ሰ/ት/ቤት ሲሆኑ 📌በአጠቃላይ እንደ አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከሃያ ሰባቱ (27) አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች 12ቱ በአንድነቱ መመሪያ መሠረት በአግባቡ የመረጡ ሲሆን ቀሪዎቹ ሰ/ት/ቤቶች በሙሉ እስከ ሰኔ 28/2018 ዓ.ም መርጠው የሚያጠናቅቁ ይሆናል።
ለአዳዲስ የሥራ አመራር አባላት 2ኛ ዙር ስልጠና ተሰጠ
Active
ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም
ለአዳዲስ የሥራ አመራር አባላት 2ኛ ዙር ስልጠና ተሰጠ
📌 በአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት  በተዘጋጀው የአዳዲስ ሥራ አመራሮች እና የቁጥጥርና ክትትል ክፍል አባላት የሚሳተፉበት የስልጠና መርሐግብር የ2ኛ ቀን ስልጣና  በ12/11/2018 ዓ.ም በመልካም ሁኔታ ተካሂዷል፡፡ አዲስ ሥራ አመራር የተመረጡ የሥራ አመራር አባላት እና የክትትል እና አፈጻጸም በአዲሱ መዋቅር ለተመረጡ እንደ አዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተዘጋጀ ሥልጠና በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ በሁለት የሥልጠና ማዕከላት ፡ 📍በሳሪስ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወአቡነ አረጋዊ ገዳም ለመደብ 1 እና 2 የተዘጋጀ ሲሆን ከአቃቂ ክ/ከተማ  6 አጥቢያዎች እንዲሁም ከንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ  7 አጥቢያዎች ለተወጣጡ 71 ሰልጣኞች '' መዋቅር" በሚል በላዕከ ሄራን መንክር ግርማ  ሥልጠናው በሚገባ ተሰጥቷል። 📍 በጃቴ መካነ ሕይወት ቅዱስ ኪዳነ ምሕረት ካቴድራል፣ በክፍለ ከተማው በሚገኙ 21 የመደብ 3 እና 4 አጥቢያዎች የተውጣጡ 89 ሰልጣኞች በ"ተግባቦት" እና "የችግር አፈታት" በሚሉ ርዕሶች በመ/ር በሃይሉ ደሳለኝ ሥልጠናው በሚገባ ተሰጥቷል። በሥልጠናው ወቅት አሰልጣኞች ያዘጋጁት የሥልጠና ሰነድ ከቀረበ በኋላ፣ ሰልጣኞች በቡድን በመከፋፈል ሰፊ ውይይት አካሂደው የራሳቸውን ልምድና ሐሳብ ተለዋውጠዋል። ለሥልጠናው ምቹ አካባቢ እንዲፈጠርም የሻይ ሰዓት መስተንግዶ በአዘጋጅ አጥቢያዎች ተሸፍኗል። ሁለቱንም ሥልጠናዎች ላስተናገዱ የአጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤት አመራሮች፣ ለአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት፣ ለአሰልጣኞች፣ ለክፍለ ከተማው ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮችና አባላት፣ እንዲሁም ሥልጠናውን በጥሩ ሥነ ምግባርና ትኩረት ለተከታተሉ ሁሉም ሰልጣኞች ከልብ ምስጋናችንን እናቀርባለን። የአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት