
ዳግማዊት አክሱም ጽዮን ማርያም
dagmawit axum debre tsion kidset Maryam
የሰንበት ት/ቤት ጥቅሙና አስፈላጊነቱ የጎላ መሆኑ በተግባር በመረጋገጡ በ1970 ዓ.ም “ሰንበት ት/ቤት” በሚል ስያሜ ሕጋዊ ሆኖ እንዲቀጥል እና በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ሰንበት ት/ቤቶች እንዲቋቋሙ የተቋቋሙትም እንዲጠናከሩ ተሻሽሎ በወጣው ቃለ ዓዋዲ እንዲጸድቅ ተደርጓል፡፡ የሰ/ት/ቤት አገልግሎትን የበለጠ ለማጠናከር ሰንበት ት/ቤቶች የሚመሩበትን መተዳደሪያ ደንብ አጽ…


Sunday School
dagmawit axum debre tsion kidset Maryam
የእኛ ተልእኮ፣ ራእይ እና ዓላማ
ዳግማዊት አክሱም ጽዮን ማርያም ለማህበረሰቡ የሚያቀርበውን የመንፈሳዊ እና ማህበራዊ አላማ ከታች በግልፅ መልኩ አቀርበናል።
<p>የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዶግማ ፣ቀኖና እና ትውፊት አውቆ የሚያሳውቅ ጠብቆ የሚያስጠብቅ በመንፈሳዊ ሕይወቱ ጠንካራ የሆነ በመንፈሳዊ ትምህርትም በዘመናዊ ትምህርትም የበሰለ በሃይማኖት እና በምግባር የታነጸ ትውልድ ማፍራት"</p>
<p>የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዶግማ፣ ቅኖና፣ እምነትና ሥርዓት ተጠብቆ ሳይበረዝ ሳይከለስ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ማድረግ<br>ማንኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ ተከታይ የሆነ ምእመን የሃይማኖቱን ሥርዓት በውል እንዲያውቅና እንዲረዳ ማድረግ።</p>
<p>መንፈሳዊነት</p><p>አገልጋይነት</p><p>ተጠያቂነት</p>
ስለ ሰንበት ት/ቤቱ
ለሁሉም እድሜ ደረጃ እምነት፣ ትምህርት እና አስተባበር ማሳደግ
ዳግማዊት አክሱም ጽዮን ማርያም
ፍኖተ ሎዛ ሰንበት ትምህርት ቤት
ስለ አመሰራረቱ
ስለ እኛ
የሰንበት ት/ቤት ጥቅሙና አስፈላጊነቱ የጎላ መሆኑ በተግባር በመረጋገጡ በ1970 ዓ.ም “ሰንበት ት/ቤት” በሚል ስያሜ ሕጋዊ ሆኖ እንዲቀጥል እና በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ውስጥ ሰንበት ት/ቤቶች እንዲቋቋሙ የተቋቋሙትም እንዲጠናከሩ ተሻሽሎ በወጣው ቃለ ዓዋዲ እንዲጸድቅ ተደርጓል፡፡ የሰ/ት/ቤት አገልግሎትን የበለጠ ለማጠናከር ሰንበት ት/ቤቶች የሚመሩበትን መተዳደሪያ ደንብ አጽድቆ ሥራ ላይ እንዲውል ያደረገ ሲሆን አሁን አስካለንበት ዘመን ድረስ ሰንበት ት/ቤቶች ይህን መመሪያ ከዋናው ቃለ ዐዋዲ ጋር በማስተባበር እየተመሩበትና ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶችን እየፈፀሙ ይገኛሉ፡፡የእኛም ሰንበት ትምህርት ቤት ይህን ዓላማ እያስፈጸመ ይገኛል።

ስለ ቤተክርስቲያኑ ታሪክ እና መግለጫ
የዳግማዊት አክሱም ጽዮን ማርያም ቤተክርስቲያን በድሮው መጠርያ ስሙ ወረዳ 24 ቀበሌ 13 በአሁኑ አጠራር ወረዳ 9 ልዩ ስሙ ጦር ኃይሎች አውግስታ ሸሚዝ ፋብሪካ አካባቢ የሚገኝ ሲሆን በዚህ ስፍራ ላይ ታቦት ለማስገባትና ህዝቡ አምልኮውን በተገቢው ቦታ ይገልጽ ዘንድ ጥቂት የማይባሉ የአካባቢው አባቶችና እናቶች በመንፈስ ቅዱስ አነሳሽነት፣ በፍቃደ እግዚአብሔር ፣የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያምን የቃል ኪዳን ታቦት ጥቅምት 24/ 1994 ዓ.ም አስገቡ።
የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
ያግኙን
የሰንበት ትምህርትቤቶች አንድነትን ለማግኘት ከፈለጉ ከታች ያሉትን አድራሻዎች በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ
ስልክ
+251922974248
ኢሜል
fenoteloza9@gmail.com
ሁኔታ
Active
አድራሻ
አድራሻ መረጃ አልተገኘም
ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እና አስተያየት ከታች ያለውን ፎርም ይጠቀሙ
Location
አካባቢ