
ለቡ ደብረታቦር በዓለወልድ እና አበ ብዙሃን አብርሃም ቤተክርስቲያን
Lebu Debre Tabor Bealewold and Abune Abrham Church
ሰንበት ትምህርት ቤታችን መዋቅራዊ አቅሟ ጎልብቶና ተደራሽነቷ ሰፍቶ ፣የመማር ማስተማር ሂደቷ አባላት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት ተዋህደው የቤተ ክርስቲያን አልኝታና መከታ እንዲሆኑና የሀገር ፍቅር እንዲኖራቸው ማድረግ


Sunday School
Lebu Debre Tabor Bealewold and Abune Abrham Church
01 • ንፋስ ስልክ ላፍቶ • አዲስ አበባ
የእኛ ተልእኮ፣ ራእይ እና ዓላማ
ለቡ ደብረታቦር በዓለወልድ እና አበ ብዙሃን አብርሃም ቤተክርስቲያን ለማህበረሰቡ የሚያቀርበውን የመንፈሳዊ እና ማህበራዊ አላማ ከታች በግልፅ መልኩ አቀርበናል።
<p> የቤተ ክርስቲያናችን ተተኪ ትውልድ ለማፍራት የሰንበት ት/ቤታችን አባላትን በተደራጀ መዋቅራዊ አንድነት፣ ወጥ በሆነው ሥርዓት ትምህርት በማስተማርና የአገልጋዮችን አቅም በማሳደግ ዘመኑን በዋጀ አሠራር በመጓዝ ቤተ ክርስቲያንን እና ሀገርን የሚያገለግሉና የሚጠብቁ አገልጋዮችን ማፍራትና ሰርቶ ማሳየት</p>
<p>የቤተክርስቲያን ዶግማ ፤ስርዓት እና ትውፊት ጠብቆ በማስጠበቅ ከትውልድ ወደ ትውልድ ማስተላለፍ ነው፡፡</p><p>የሰንበት ት/ቤቱ አባላት በቤተክርስቲያን በዕውቀታቸው በገንዘባቸው በጊዜያቸው እንዲያገለግሉ ሁኔታቸውን ማመቻቸት፡፡</p>
<p>1.እግዚአብሔርን መፍራት</p><p>2.በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነት ማመን</p><p>3.በመላዕክትና በቅዱሳን አማላጅነት ማመን</p><p>4.ለሰው ሁሉ ክብር መስጠት</p><p>5.በተግባር የተገለጠና በፍቅር አገልግሎት መስጠት</p><p>6. ዘመኑን ማወጀት</p><p><br><br></p>
ስለ ሰንበት ት/ቤቱ
ለሁሉም እድሜ ደረጃ እምነት፣ ትምህርት እና አስተባበር ማሳደግ
ለቡ ደብረታቦር በዓለወልድ እና አበ ብዙሃን አብርሃም ቤተክርስቲያን
ኆኅተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
ስለ አመሰራረቱ
ስለ እኛ
ሰንበት ትምህርት ቤታችን መዋቅራዊ አቅሟ ጎልብቶና ተደራሽነቷ ሰፍቶ ፣የመማር ማስተማር ሂደቷ አባላት በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት ተዋህደው የቤተ ክርስቲያን አልኝታና መከታ እንዲሆኑና የሀገር ፍቅር እንዲኖራቸው ማድረግ

ስለ ቤተክርስቲያኑ ታሪክ እና መግለጫ
ሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቱን ትውልድ በአምልኮተ እግዚአብሔርን አፅንቶ በሃይማኖትና በምግባር ከማኖርም ባሻገር ለቤተ ክርስቲያን ቀናኢ የሆኑ አገልጋዮችን አፍርቷል፤ በማፍራት ላይም ይገኛል። ሰንበት ትምህርት ቤት በዕለተ ሰንበትና አበይት በዓላት ወቅት ያሬዳዊ መዝሙራትን ከማቅረብም በላይ ዲያቆናትን፣ ቀሳውስትን፣ ቆሞሳትን፣ ጳጳሳትን፣ መምህራነ ወንጌልን፣ ሰባኪያንን እና በልዩ ልዩ አገልግሎት ላይ የሚፋጠኑ ዘመኑን የዋጁ አገልጋዮችን ለቤተ ክርስቲያናችን አበርክቷል። ይህ አገልግሎት እንዳይቋረጥና ቤተ ክርስቲያን ለትውልድ ሁሉ ከነሙሉ ክብሯ ትተላለፍ ዘንድ በያለንበት አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ሰንበት ትምህርት ቤትን ማጠናከር የዘወትር ተግባር ሊሆን ይገባል።
የለቡ ደብረ ታቦር በዓለወልድ እና አበ ብዙኃን አብርሃም ቤተ ክርስቲያን በአካባቢው በሚገኙ የመሬት ባለቤቶች በተሰጠ ቦታ ላይ ቆርቆሮ በቆርቆሮ በሆነ መቃኞ ተሰርቶ ታቦተ እግዚአብሔር ወልድን በማስገባት ጥር 20 ቀን 1995 ዓ.ም የተቋቋመ ቤተክርስቲያን ነው፡፡ ታቦተ እግዚአብሔር ወልድ በቦታው እንዲመጣ ምክንያት የሆነው በአካባቢው ከ1937 ዓ.ም ጀምሮ የተቋቋመ የበዓለወልድ እድር ነው።
በቆርቆሮ የተሰራው መቃኞ ለ4 ዓመታት ካገለገለ በኋላ ስመ ክርስትናቸው ብርሃነ ገብርኤል የተባሉ ባለሀብት ምዕመን ደረጃውን የጠበቀ ቤተክርስቲያን ለመስራት በመወሰንና ይኽንኑ ለሚመለከታቸው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የበላይ ሐላፊዎች በማሳወቅ ተፈቅዶላቸው አሁን ያለውን ህንጻ ቤተክርስቲያን አንጸዋል።
የግንባታ ሥራው ተጀምሮ ከተጠናቀቀ በኋላ በወቅቱ በነበሩት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ፓትሪያሪክ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ነሐሴ 28 ቀን 1999 ዓ.ም ተባርኮ ጽላቱ በአማረ ሁኔታ ደረጃውን ጠብቆ ወደተሰራው አዲስ ህንፃ እንዲገባ ተደረገ፡፡
የምንሰጣቸው አገልግሎቶች
ያግኙን
የሰንበት ትምህርትቤቶች አንድነትን ለማግኘት ከፈለጉ ከታች ያሉትን አድራሻዎች በመጠቀም ማግኘት ይችላሉ
ስልክ
+251943172591
ኢሜል
hohitehiwot@gmail.com
ሁኔታ
Active
አድራሻ
01 • ንፋስ ስልክ ላፍቶ • አዲስ አበባ
ለማንኛውም አይነት ጥያቄ እና አስተያየት ከታች ያለውን ፎርም ይጠቀሙ
Location
አካባቢ